Wednesday, July 23, 2014

አንዳንድ ጊዜኮ የምናማርረው ችግር ስለደረሰብን ብቻ ሳይሆን ያለንን ስለማናውቀው ጭምር ነው፡፡ ችግር በራሱ ችግር አይደለም፡፡ ችግር ችግር የሚሆነው መፍትሔ መስጠት ለማይችል ሰው ብቻ ነው፡፡ መፍትሔ መስጠት ለለመደ ችግር ትምህርት ቤት ነው፡፡ ችግርኮ የፍች፣ የመለያየት፣ የጠብ፣ የኩርፊያ፣ የክስ፣ የመልቀቂያ፣ መንገድ የሚሆነው ለዐቅመ ቢስ ሰው ነው፡፡ ለብርቱ ሰው ግን ሞት የትንሣኤ መቅድም ነው፡፡
የሌለህን ነገር ብቻ ካሰብክ ያለህንም ታጣዋለህ፡፡ ያለህን ነገር ካሰብክ ግን የሌለህንም ታገኘዋለህ፡፡

No comments:

Post a Comment