አንዳንድ
ጊዜኮ የምናማርረው ችግር ስለደረሰብን ብቻ ሳይሆን ያለንን ስለማናውቀው ጭምር ነው፡፡ ችግር በራሱ ችግር
አይደለም፡፡ ችግር ችግር የሚሆነው መፍትሔ መስጠት ለማይችል ሰው ብቻ ነው፡፡ መፍትሔ መስጠት ለለመደ ችግር
ትምህርት ቤት ነው፡፡ ችግርኮ የፍች፣ የመለያየት፣ የጠብ፣ የኩርፊያ፣ የክስ፣ የመልቀቂያ፣ መንገድ የሚሆነው ለዐቅመ
ቢስ ሰው ነው፡፡ ለብርቱ ሰው ግን ሞት የትንሣኤ መቅድም ነው፡፡
የሌለህን ነገር ብቻ ካሰብክ ያለህንም ታጣዋለህ፡፡ ያለህን ነገር ካሰብክ ግን የሌለህንም ታገኘዋለህ፡፡
የሌለህን ነገር ብቻ ካሰብክ ያለህንም ታጣዋለህ፡፡ ያለህን ነገር ካሰብክ ግን የሌለህንም ታገኘዋለህ፡፡
No comments:
Post a Comment