Sunday, July 27, 2014

ከንቲባው

ለመለወጥ ጥረት ስለምታደርግ ነፍስ አባ ዮሐንስ ሐጺር ለአንድ መነኰሴ ያስተማረበት ምሳሌ

እንደሚከተለው ተጽፎ ይገኛል፡-“በከተማ መካከል ብዙ ወዳጆች ያሏት አንዲት ቆንጆ ሴተኛ አዳሪ ነበረች፡፡

የከተማዋ ከንቲባ ወደ እርሷ ቀርቦ፡- መልካም ሴት እንደምትሆኚ ቃል ከገባሽልኝ አሁኑኑ አገባሻለሁ ይላታል፡፡

እርሷም በሐሳቡ ተስማምታ ቃል ስለገባችለት ወደ ቤቱ ይዟት ሄደ፡፡

ወዳጆቿ ድጋሚ ሊያገኟት ስለ ፈለጉ እንዲህ እያሉ ይመካከሩ ነበር፡- የከተማው ከንቲባ ወዳጃችንን ወደ ቤቱ ወስዷታል፡፡

በግልጽ ወደ ቤቱ ከሄድን ስለሚያውቅብንና ስለሚያስፈርድብን በቤቱ ጓሮ ዞረን እናፏጭላት፡፡ የፉጨታችንን ድምጽ ለይታ ስለምታውቃቸው ከቤቷ ወርዳ ትመጣለች፡፡ ለማንኛውም ግን እርሷ ትምጣልን እንጂ እኛ አንጣላም አሉ፡፡

በመጨረሻ እንደተመካከሩት በቤቱ ጓሮ ዞረው ሲያፏጩላት ጀሮዎቿ ቆሙ፡፡ ይሁን እንጂ ወደ እነርሱ ልትወርድ ስላልፈለገች ፈጠን ብላ ወደ እንግዳ መቀበያው አዳራሽ ገባችና በሮቿን ዘጋግታ ከውስጥ ተቀመጠች፡፡

ልክ እንደዚሁ ነፍሳችን በዚህች ሴት ስትመሰል ወዳጆቿ ደግሞ ምኞቶቻችን ይመስላሉ፡፡

ከንቲባው የሚመሰለው በምንወደው በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ነው፡፡

በቤቱ ውስጥ ያለው የእንግዳ መቀበያ አዳራሽ በዘላለማዊ ቤታችን ወይም በመንግሥተ ሰማያት ሲመሰል

የሚያፋጩላት ሰዎች ደግሞ በርኩሳን መናፍስት ይመሰላሉ፡፡

በመጨረሻም ይህን ምሳሌ ነፍሳችን ሁል ጊዜ እግዚአብሔርን ከተጠጋች በእርሱ ኃይል እንደምትኖር ያስረዳናል፡፡”

እግዚአብሔር አምላክ አስተዋይ ልቦና ያድለን አሜን !!!

No comments:

Post a Comment