Sunday, July 27, 2014

የቅዱስ ያሬድ ታሪክ

የቅዱስ ያሬድ ታሪክ

ቅዱስ ያሬድ በ505 ዓ/ም በአክሱም ተወለደ። አባቱ አብዩድ ወይም ይስሐቅ እናቱም ክርስቲና ወይም ታውክልያ ይባሉ ነበር። የነርሱም ሀገራቸውና ርስታቸው አክሱም ነበር። ቅዱስ ያሬድ በተወለደ በ7 ዓመቱ አባቱ ስለሞተ እናቱ ክርስቲና የአክሱም ገበዝ ለነበረው ለአጎቱ ለጌዲዎን እንዲያሳድገውና እንዲያስተምረው አደራ ብላ ሰጠችው። ከጌዴዎንም ቤት 25 ዓመት እስኪሆነው እየተማረ አደገ። ከዚያም መፃህፍትን ማለት ብሉይንና አዲስን ተማረ። ከዚህም በኋላ መምህሩ (አጎቱ) ጌዴዎን ሲሞት እርሱ ተተክቶ የመጽሐፍ መምህር ሆነ። በዚህም ጊዜ በዲቁና ሚስት አግብቶ ልጆችን ወለደ። ቀጥሎም ቄስ ሆነ።

በእርሱም ዘመን 9ኙ ቅዱሳን ከውጭ አገር በችግር ምክንያት ተሰደው ስለመጡ፤ ይህም ማለት በቁስጥንጥንያ መንግሥት ዮስጥንያኖስ ዩስቲኒያኖስ በነገሠበት ከ527 ዓ/ም እስ ከ 565 ዓ/ም ድረስ በምሥራቅ ቤተ ክርስቲያን ውስጥ በአንድ ባሕርይና በሁለት ባሕርይ ወገኖች ውስጥ ብዙ ሁከትና ፍጅት ስለነበረ ከዚያ በመሸሽ የመጡ ካህናትና መነኮሳት ስለነበሩ ከእነርሱም አንዱ በአክሱም ከተማ አጠገብ የነበረው አባ ጰንጠሊዎን ስለነበር፤ ቅዱስ ያሬድ እየተመላለሰ የውጭውን አገር ቤት ክርስቲያን ባሕልና ሥርዓት ይጠይቀው ነበር ይባላል።

ከዚያም በኋላ ቅዱስ ያሬድ የውጭውን አገር ቤት ክርስቲያን ባሕልና ሥርዓት ለመጎብኘት ሁለት ጊዜ ተመላልሼ የሮምን ቤተ ክርስቲያን፤ 2ኛይቱን ሮም የተባለችውን የምሥራቅና የቁስጥንጥንያን ቤተ ክርስቲያን ጎበኘሁ’ ሲል በመዝሙሩ እርሱ ራሱ ገልፆልናል። (ወሪድዬ ብሔረ ሮሜ ለቤተ ክርስቲያን ርኢክዋ አእመርክዋ አፍቀርክዋ ከመ እኅትየ ሠናይ ሐለይኩ፤ እምድኅረ ጉንዱይ ዓመታት ወእምዝ እምድኅረ ኅዳጥ መዋዕል ካዕበ ርኢክዋ ወትትሐጸብ በፈለገ ጤግሮስ) እንደዚህ እያለ የውጭውን አገር ቤተ ክርስቲያን ሲያመሰግን ይገኛል።

ከሱ በፊት በኢትዮጵያ ቤተክርስቲያን ደንበኛ የሆነ ቅኔና ዜማ ትምህርት ስለሌለ ደንበኛ የሆነ ቅኔና ዜማ ለማስገኘት ተዘጋጀ። የድርጅቱም መጀመሪያ ይህ ነበር። ሃሌ ሉያ ለአብ ሃሌ ሉያ ለወልድ ሃሌ ሉያ ወለመንፈስ ቅዱስ፤ ቀዳሚሃ ለጽዮን ሰማየ ሣረረ ወበዳግም አርአዮ ለሙሴ ዘከመ ይገብር ግብራ ለደብተራ ብሎ ከነበሩት ከብሉይና ከሐዲስ ሊቃውንት አንዱ እርሱ ስለ ነበርና ለኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያንም ብዙ አሳብ ስለነበረው ከብሉይና ከሐዲስ፣ ከሊቃውንት መጻሕፍትም ከነአትናቴዎስ ከነቄርሎስ ከነዮሐንስ አፈወርቅ መጻሕፍት ለምስጋናና ለጸሎት የተስማሙትን ቃላት እየመረጠና እያቀና በአራቱ ክፍለ ዘመን፣ በመፀውና በሐጋይ በጸደይና በክረምት እንዲነገር አድርጎ ወስኖ አዘጋጀ።

የመጽሐፉ (የድርሰቱ) ስም ድጓ ተባለ። ድጓ ማለትም በአክሱምና በአድዋ ቋንቋ (በትግርኛ) ደጉዓ ማለት መዝሙረ ኃዘን፥ የኃዘን ዜማ፥ ማለት ነው። – ሙሾ። የዜማውን ዓይነት በሦስት ክፍል ወስኖ ተናግሮታል። እነርሱም ግዕዝ፣ ዕዝል፣ ዓራራይ ይባላሉ። ግዕዝ ማለትም አንደኛ በመጀመሪያ የተገኘ ማለት ነው፤ ዕዝል ማለትም ሁለተኛ ሆኖ ከግዕዙ ጋር ተደርቦ፣ ተጨምሮ (ታዝሎ) የሚነገር ማለት ነው። ዓራራይ ማለትም ሦስተኛ ተጨማሪ ሆኖ አራኅራኂ፣ ርኅራኄ/አሳዛኝ ልብን የሚመስጥና ደስ የሚያሰኝ ማለት ነው። ይህን ድርሰቱን ያዘጋጀበት ዘመን ከ540 ዓ/ም ሲሆን የመጨረሻ ልጁ አፄ ገብረ መስቀል መንግሥቱን ወረሰ።

አፄ ገብረ መስቀልና አባ አረጋዊ ቅዱስ ያሬድ እነዚህ ሦስቱ በአንድነት እንደነበሩ ታሪከ ነገሥቱና ገድለ አረጋዊ ይገልጽልናል። አቡነ አረጋዊ የደብረ ዳሞን ተራራ አቀማመጥ አይተው ደስ ስላላቸው፣ ንጉሡ አፄ ገብረ መስቀል በዚሁ ተራራ ላይ እንዲኖሩበትና እንዲጸልዩበት ፈቀደላቸው። እርሳቸውም ይህንን ተራራ ከተረከቡ በኋላ በተራራው ላይ የጸሎት ቤት ስለሌለ ንጉሡ አፄ ገብረ መስቀልን አንድ ቤተ ክርስቲያን እንዲሠራላቸው ለመኑት። ንጉሡም ቤተክርስቲያን ልሠራ የምችልበትን ሥፍራ መርጠው ያመልክቱኝ ብሎ ነገራቸው አቡነ አረጋዊም ተነሥተው ዞረው ቦታውን መርጠው አሳዩት።

ከዚህ በኋላ ንጉሡ በአዋጅና በትዕዛዝ ድንጋዩና እንጨቱ እየተሰበሰበ በከብትና በሠረገላ እየተጋዘ ተሰበሰበና ከታች ወደ ተራራው ላይ ወጥቶ ተሠራና የቤተ ክርስቲያኑ ሥራ በሁለት ዓመት አለቀ። ባለቀም ጊዜ የቤተክርስቲያኑ ሥራ ተመልካቾችን አስደነቀ። ለዚሁም ቤተክርስቲያን ልዩ ልዩ የሆኑ አልባሳት፣ የብርና የወርቅ የተደጎሱና የተከፈፉ መጻሕፍትን አበረከቱ። ከማኅበረ በኩር የመጣውን የእመቤታችንን የቅድስት ድንግል ማርያምን ጽላት አግብተው አቡነ አረጋዊ ባርከውና ቀድሰው ንጉሡና ጳጳሱ ቆረቡ። ከዚያም አፄ ገብረ መስቀል በተራራው ላይና በግርጌ ላሉት ሠራዊት ግብር አብልተው ነዳያን ሁሉ ጠገቡ።

ከዚህ በኋላ ቅዱስ ያሬድ በአክሱም ሲያስተምር ሳለ በንጉሡ አፄ ገብረመስቀልና አቡነ አረጋዊ፥ ወደዚህ ተራራ መጥቶ ቤተክርስቲያኑን እንዲጎበኝና እንዲዘምር ተጠርቶ ሲመጣ ከተራራው ሥር ሲደርስ የአቡነ አረጋዊን ደቀመዛሙርት ማትያስና ዮሴፍ የሚባሉትን ከወንዝ ዳር ዓሣ ሲያጠምዱ አግኝቶ ዳኅንኑ ዝስኩ አረጋዊ አቡክሙ (ይህ አረጋዊ አባታችሁ ደህና ነው?) ብሎ ጠየቃቸው። እነርሱም ደኅንነታቸውን ነገሩት። ከዚያም ቅዱስ ያሬድ ወደ ተራራው ላይ ወጥቶ ከአቡነ አረጋዊ ጋር በመንፈሳዊ አምኃ በፍቅር ተገናኙ ወደ ቤተክርስቲያኑም ሄዶ 3 ጊዜ ሰግዶ ከተሳለመ በኋላ የሕንጻውን ማማር በአድናቆት ተመልክቶ ከፍ ባለ የዜማ ድምፅ እያጉረመረመ እንዲህ ሲል ዘመረ።

‘ይሄውፅዋ መላዕክት እንተ በሰማያት ይሄውፅዋ መላዕክት እስመ ማኅደረ መለኮት ፆድክዋ ፆድክዋ ፆድክዋ ወርኢኩ ሥነ ሕንፄሃ ለቅድስት ቤተክርስቲያን ምሥአል ወምስጋድ ወምሥትስራየ ኃጢአት ይዕቲ ቅድስት ደብተራ።’ የሚለውን መዝሙር ከዘመረ በኋላ ስምንት ቀን ያህል ከአቡነ አረጋዊ ጋር ሰንብቶ ንጉሡ ወደ አለበት ወደ አኩሱም ተመልሶ ሲገባ አንቀጸ ብርሃን ተብሎ የተሰየመውን ድርሰትን ቅድስት ወብፅዕት ብሎ በዜማ ደረሰ። ከዚህ በኋላ ንጉሡ አፄ ገብረ መስቀልና አቡነ አረጋዊ ከቅዱስ ያሬድ ጋር አብረው ወደ ሌላ ጠቅላይ ግዛት ጉብኝት ሄዱ። ከዚያም በአንዱ ደሴት ላይ የቅዱስ ቂርቆስን ቤተ ክርስቲያን ሠርተው ተቀመጡ። በዚያም ቦታ ቅዱስ ያሬድ ሁለት ዓመት አስተማረ። እርሱ እራሱ ጻፈው የሚባል ድጓ ምልክት የሌለው ዛሬ በዚሁ ደሴት በጣና ቂርቆስ ይገኛል።

ከዚህም ደሴት ከጣና ቂርቆስ ተነሥተው ንጉሡና አቡነ አረጋዊ ቅዱስ ያሬድም ወደ ደጋው ወደ ጋይንት ወጡ። በዚያም አንድ ትልቅ ተራራ አግኝተው መውጫው ጠፍቶባቸው ሲጨነቁ አንድ ከእግዚአብሔር የታዘዘ መልዕክተኛ መጥቶ አቡነ አረጋዊን (ዙር አባ መንገለ ምሥራቅ) አባ መውጫውን በምሥራቅ በኩል ታገኘዋለህ ሲል አመለከታቸውና ሦስቱም ተያይዘው ወደ ተራራው ላይ ወጡ። በዚሁ ተራራ ላይ የእመቤታችንን ቤተ ክርስቲያን ሠሩ። የተራራውም ስም እስከ ዛሬ ድረስ ዙር አምባ ተብሎ ይጠራል።ቅዱስ ያሬድ በዚሁ ተራራ ላይ ሦስት ዓመት ዝማሬ መዋሥዕት የተባለውን መዝሙር አስተምሯል። ይህም ቦታ እስከ ዛሬ ድረስ የዝማሬና የመዋሥዕት ምስክር ቦታ ሆኖ ይኖራል።

ከዚህ በኋላ ቅዱስ ያሬድ ወደ አክሱም ተመልሶ ለሥጋ ወደሙ ጸሎት የሚያገለግሉትን 14ቱን ቅዳሴዎች በዜማ ተናገረ። ቅዳሴውን በዜማ የተናገረበት ቦታ መደባይታብር ይባላል። ይህም መደባይታብር የሚባለው ቦታ ለአክሱም ሰሜን ሆኖ ከአክሱም ግማሽ ቀን ያህል በእግር ያስኬዳል። ከዚያም ወደ ሰሜን ተራራዎች ወደ ጠለምት ሔዶ ምዕራፍ የተባለውን የዳዊትን መዝሙር ተናገረ። ከዚህ በኋላ ወደ ወገራና ወደ አገው እየዞረ ካስተማረ በኋላ ከሰሜን ተራራዎች ሥር ባሉት በአንዱ ገዳም ውስጥ በብሕትውና ከቆየ በኋላ በሰሜን ምሥራቅ ባለው ሸዋ ውስጥ በ571 ዓ/ም ግንቦት 11 ቀን አረፈና ተቀበረ።

ከዚህ በኋላ የእርሱ ደቀመዛሙርት ሳዊሮስና ሳንድሮስ በልዳዶስ የሚባሉት ከርሱ የተማሩትን የዜማ ባሕልና ሥርዓት በትግሬና በሰሜን አውራጃ እየተዘዋወሩ በየገዳማቱ ሁሉ ስለአስተማሩ የቅዱስ ያሬድ ድርሰት እስከ ዛሬ ድረስ ጸንቶ ይኖራል።

ምንጭ:“የቅዱስ ያሬድ ታሪክና የዜማው ምልክቶች” ግንቦት 15/ 1959 በትንሳኤ ዘጉባኤ ማተሚያ ቤት የታተመ መጽሐፍ

ቅዱስ ያሬድ በ505 ዓ/ም በአክሱም ተወለደ። አባቱ አብዩድ ወይም ይስሐቅ እናቱም ክርስቲና ወይም ታውክልያ ይባሉ ነበር። የነርሱም ሀገራቸውና ርስታቸው አክሱም ነበር። ቅዱስ ያሬድ በተወለደ በ7 ዓመቱ አባቱ ስለሞተ እናቱ ክርስቲና የአክሱም ገበዝ ለነበረው ለአጎቱ ለጌዲዎን እንዲያሳድገውና እንዲያስተምረው አደራ ብላ ሰጠችው። ከጌዴዎንም ቤት 25 ዓመት እስኪሆነው እየተማረ አደገ። ከዚያም መፃህፍትን ማለት ብሉይንና አዲስን ተማረ። ከዚህም በኋላ መምህሩ (አጎቱ) ጌዴዎን ሲሞት እርሱ ተተክቶ የመጽሐፍ መምህር ሆነ። በዚህም ጊዜ በዲቁና ሚስት አግብቶ ልጆችን ወለደ። ቀጥሎም ቄስ ሆነ።

በእርሱም ዘመን 9ኙ ቅዱሳን ከውጭ አገር በችግር ምክንያት ተሰደው ስለመጡ፤ ይህም ማለት በቁስጥንጥንያ መንግሥት ዮስጥንያኖስ ዩስቲኒያኖስ በነገሠበት ከ527 ዓ/ም እስ ከ 565 ዓ/ም ድረስ በምሥራቅ ቤተ ክርስቲያን ውስጥ በአንድ ባሕርይና በሁለት ባሕርይ ወገኖች ውስጥ ብዙ ሁከትና ፍጅት ስለነበረ ከዚያ በመሸሽ የመጡ ካህናትና መነኮሳት ስለነበሩ ከእነርሱም አንዱ በአክሱም ከተማ አጠገብ የነበረው አባ ጰንጠሊዎን ስለነበር፤ ቅዱስ ያሬድ እየተመላለሰ የውጭውን አገር ቤት ክርስቲያን ባሕልና ሥርዓት ይጠይቀው ነበር ይባላል።

ከዚያም በኋላ ቅዱስ ያሬድ የውጭውን አገር ቤት ክርስቲያን ባሕልና ሥርዓት ለመጎብኘት ሁለት ጊዜ ተመላልሼ የሮምን ቤተ ክርስቲያን፤ 2ኛይቱን ሮም የተባለችውን የምሥራቅና የቁስጥንጥንያን ቤተ ክርስቲያን ጎበኘሁ’ ሲል በመዝሙሩ እርሱ ራሱ ገልፆልናል። (ወሪድዬ ብሔረ ሮሜ ለቤተ ክርስቲያን ርኢክዋ አእመርክዋ አፍቀርክዋ ከመ እኅትየ ሠናይ ሐለይኩ፤ እምድኅረ ጉንዱይ ዓመታት ወእምዝ እምድኅረ ኅዳጥ መዋዕል ካዕበ ርኢክዋ ወትትሐጸብ በፈለገ ጤግሮስ) እንደዚህ እያለ የውጭውን አገር ቤተ ክርስቲያን ሲያመሰግን ይገኛል።

ከሱ በፊት በኢትዮጵያ ቤተክርስቲያን ደንበኛ የሆነ ቅኔና ዜማ ትምህርት ስለሌለ ደንበኛ የሆነ ቅኔና ዜማ ለማስገኘት ተዘጋጀ። የድርጅቱም መጀመሪያ ይህ ነበር። ሃሌ ሉያ ለአብ ሃሌ ሉያ ለወልድ ሃሌ ሉያ ወለመንፈስ ቅዱስ፤ ቀዳሚሃ ለጽዮን ሰማየ ሣረረ ወበዳግም አርአዮ ለሙሴ ዘከመ ይገብር ግብራ ለደብተራ ብሎ ከነበሩት ከብሉይና ከሐዲስ ሊቃውንት አንዱ እርሱ ስለ ነበርና ለኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያንም ብዙ አሳብ ስለነበረው ከብሉይና ከሐዲስ፣ ከሊቃውንት መጻሕፍትም ከነአትናቴዎስ ከነቄርሎስ ከነዮሐንስ አፈወርቅ መጻሕፍት ለምስጋናና ለጸሎት የተስማሙትን ቃላት እየመረጠና እያቀና በአራቱ ክፍለ ዘመን፣ በመፀውና በሐጋይ በጸደይና በክረምት እንዲነገር አድርጎ ወስኖ አዘጋጀ።

የመጽሐፉ (የድርሰቱ) ስም ድጓ ተባለ። ድጓ ማለትም በአክሱምና በአድዋ ቋንቋ (በትግርኛ) ደጉዓ ማለት መዝሙረ ኃዘን፥ የኃዘን ዜማ፥ ማለት ነው። – ሙሾ። የዜማውን ዓይነት በሦስት ክፍል ወስኖ ተናግሮታል። እነርሱም ግዕዝ፣ ዕዝል፣ ዓራራይ ይባላሉ። ግዕዝ ማለትም አንደኛ በመጀመሪያ የተገኘ ማለት ነው፤ ዕዝል ማለትም ሁለተኛ ሆኖ ከግዕዙ ጋር ተደርቦ፣ ተጨምሮ (ታዝሎ) የሚነገር ማለት ነው። ዓራራይ ማለትም ሦስተኛ ተጨማሪ ሆኖ አራኅራኂ፣ ርኅራኄ/አሳዛኝ ልብን የሚመስጥና ደስ የሚያሰኝ ማለት ነው። ይህን ድርሰቱን ያዘጋጀበት ዘመን ከ540 ዓ/ም ሲሆን የመጨረሻ ልጁ አፄ ገብረ መስቀል መንግሥቱን ወረሰ።

አፄ ገብረ መስቀልና አባ አረጋዊ ቅዱስ ያሬድ እነዚህ ሦስቱ በአንድነት እንደነበሩ ታሪከ ነገሥቱና ገድለ አረጋዊ ይገልጽልናል። አቡነ አረጋዊ የደብረ ዳሞን ተራራ አቀማመጥ አይተው ደስ ስላላቸው፣ ንጉሡ አፄ ገብረ መስቀል በዚሁ ተራራ ላይ እንዲኖሩበትና እንዲጸልዩበት ፈቀደላቸው። እርሳቸውም ይህንን ተራራ ከተረከቡ በኋላ በተራራው ላይ የጸሎት ቤት ስለሌለ ንጉሡ አፄ ገብረ መስቀልን አንድ ቤተ ክርስቲያን እንዲሠራላቸው ለመኑት። ንጉሡም ቤተክርስቲያን ልሠራ የምችልበትን ሥፍራ መርጠው ያመልክቱኝ ብሎ ነገራቸው አቡነ አረጋዊም ተነሥተው ዞረው ቦታውን መርጠው አሳዩት።

ከዚህ በኋላ ንጉሡ በአዋጅና በትዕዛዝ ድንጋዩና እንጨቱ እየተሰበሰበ በከብትና በሠረገላ እየተጋዘ ተሰበሰበና ከታች ወደ ተራራው ላይ ወጥቶ ተሠራና የቤተ ክርስቲያኑ ሥራ በሁለት ዓመት አለቀ። ባለቀም ጊዜ የቤተክርስቲያኑ ሥራ ተመልካቾችን አስደነቀ። ለዚሁም ቤተክርስቲያን ልዩ ልዩ የሆኑ አልባሳት፣ የብርና የወርቅ የተደጎሱና የተከፈፉ መጻሕፍትን አበረከቱ። ከማኅበረ በኩር የመጣውን የእመቤታችንን የቅድስት ድንግል ማርያምን ጽላት አግብተው አቡነ አረጋዊ ባርከውና ቀድሰው ንጉሡና ጳጳሱ ቆረቡ። ከዚያም አፄ ገብረ መስቀል በተራራው ላይና በግርጌ ላሉት ሠራዊት ግብር አብልተው ነዳያን ሁሉ ጠገቡ።

ከዚህ በኋላ ቅዱስ ያሬድ በአክሱም ሲያስተምር ሳለ በንጉሡ አፄ ገብረመስቀልና አቡነ አረጋዊ፥ ወደዚህ ተራራ መጥቶ ቤተክርስቲያኑን እንዲጎበኝና እንዲዘምር ተጠርቶ ሲመጣ ከተራራው ሥር ሲደርስ የአቡነ አረጋዊን ደቀመዛሙርት ማትያስና ዮሴፍ የሚባሉትን ከወንዝ ዳር ዓሣ ሲያጠምዱ አግኝቶ ዳኅንኑ ዝስኩ አረጋዊ አቡክሙ (ይህ አረጋዊ አባታችሁ ደህና ነው?) ብሎ ጠየቃቸው። እነርሱም ደኅንነታቸውን ነገሩት። ከዚያም ቅዱስ ያሬድ ወደ ተራራው ላይ ወጥቶ ከአቡነ አረጋዊ ጋር በመንፈሳዊ አምኃ በፍቅር ተገናኙ ወደ ቤተክርስቲያኑም ሄዶ 3 ጊዜ ሰግዶ ከተሳለመ በኋላ የሕንጻውን ማማር በአድናቆት ተመልክቶ ከፍ ባለ የዜማ ድምፅ እያጉረመረመ እንዲህ ሲል ዘመረ።

‘ይሄውፅዋ መላዕክት እንተ በሰማያት ይሄውፅዋ መላዕክት እስመ ማኅደረ መለኮት ፆድክዋ ፆድክዋ ፆድክዋ ወርኢኩ ሥነ ሕንፄሃ ለቅድስት ቤተክርስቲያን ምሥአል ወምስጋድ ወምሥትስራየ ኃጢአት ይዕቲ ቅድስት ደብተራ።’ የሚለውን መዝሙር ከዘመረ በኋላ ስምንት ቀን ያህል ከአቡነ አረጋዊ ጋር ሰንብቶ ንጉሡ ወደ አለበት ወደ አኩሱም ተመልሶ ሲገባ አንቀጸ ብርሃን ተብሎ የተሰየመውን ድርሰትን ቅድስት ወብፅዕት ብሎ በዜማ ደረሰ። ከዚህ በኋላ ንጉሡ አፄ ገብረ መስቀልና አቡነ አረጋዊ ከቅዱስ ያሬድ ጋር አብረው ወደ ሌላ ጠቅላይ ግዛት ጉብኝት ሄዱ። ከዚያም በአንዱ ደሴት ላይ የቅዱስ ቂርቆስን ቤተ ክርስቲያን ሠርተው ተቀመጡ። በዚያም ቦታ ቅዱስ ያሬድ ሁለት ዓመት አስተማረ። እርሱ እራሱ ጻፈው የሚባል ድጓ ምልክት የሌለው ዛሬ በዚሁ ደሴት በጣና ቂርቆስ ይገኛል።

ከዚህም ደሴት ከጣና ቂርቆስ ተነሥተው ንጉሡና አቡነ አረጋዊ ቅዱስ ያሬድም ወደ ደጋው ወደ ጋይንት ወጡ። በዚያም አንድ ትልቅ ተራራ አግኝተው መውጫው ጠፍቶባቸው ሲጨነቁ አንድ ከእግዚአብሔር የታዘዘ መልዕክተኛ መጥቶ አቡነ አረጋዊን (ዙር አባ መንገለ ምሥራቅ) አባ መውጫውን በምሥራቅ በኩል ታገኘዋለህ ሲል አመለከታቸውና ሦስቱም ተያይዘው ወደ ተራራው ላይ ወጡ። በዚሁ ተራራ ላይ የእመቤታችንን ቤተ ክርስቲያን ሠሩ። የተራራውም ስም እስከ ዛሬ ድረስ ዙር አምባ ተብሎ ይጠራል።ቅዱስ ያሬድ በዚሁ ተራራ ላይ ሦስት ዓመት ዝማሬ መዋሥዕት የተባለውን መዝሙር አስተምሯል። ይህም ቦታ እስከ ዛሬ ድረስ የዝማሬና የመዋሥዕት ምስክር ቦታ ሆኖ ይኖራል።

ከዚህ በኋላ ቅዱስ ያሬድ ወደ አክሱም ተመልሶ ለሥጋ ወደሙ ጸሎት የሚያገለግሉትን 14ቱን ቅዳሴዎች በዜማ ተናገረ። ቅዳሴውን በዜማ የተናገረበት ቦታ መደባይታብር ይባላል። ይህም መደባይታብር የሚባለው ቦታ ለአክሱም ሰሜን ሆኖ ከአክሱም ግማሽ ቀን ያህል በእግር ያስኬዳል። ከዚያም ወደ ሰሜን ተራራዎች ወደ ጠለምት ሔዶ ምዕራፍ የተባለውን የዳዊትን መዝሙር ተናገረ። ከዚህ በኋላ ወደ ወገራና ወደ አገው እየዞረ ካስተማረ በኋላ ከሰሜን ተራራዎች ሥር ባሉት በአንዱ ገዳም ውስጥ በብሕትውና ከቆየ በኋላ በሰሜን ምሥራቅ ባለው ሸዋ ውስጥ በ571 ዓ/ም ግንቦት 11 ቀን አረፈና ተቀበረ።

ከዚህ በኋላ የእርሱ ደቀመዛሙርት ሳዊሮስና ሳንድሮስ በልዳዶስ የሚባሉት ከርሱ የተማሩትን የዜማ ባሕልና ሥርዓት በትግሬና በሰሜን አውራጃ እየተዘዋወሩ በየገዳማቱ ሁሉ ስለአስተማሩ የቅዱስ ያሬድ ድርሰት እስከ ዛሬ ድረስ ጸንቶ ይኖራል።

ምንጭ:“የቅዱስ ያሬድ ታሪክና የዜማው ምልክቶች” ግንቦት 15/ 1959 በትንሳኤ ዘጉባኤ ማተሚያ ቤት የታተመ መጽሐፍ

No comments:

Post a Comment