Sunday, July 27, 2014

ገዳማዊ ህይወት

==> በኢትዮጵያ የመጀመሪያው ገዳም አቡነ አረጋዊ የገደሙት ደብረ ዳሞ (ዙር አባ) ነው። በዚህ ገዳም አባታችን አቡነ አረጋዊ ለሠራዊቱ የሚሆን ውኃ እንዲፈልቅ በሚጸልዩበት ጊዜ 40 ምንጭ ፈልቋል።

==> በዓለም የመጀመሪያው ባህታዊ አባ ጳውሊ ሲሆን በዓለም የመጀመሪያውን ገዳም የገደመው ደግሞ አባ እንጦንስ ነው።

==> አባ ጳውሊ ከወንድሙ ጋር የአባታቸውን ንብረት በሚካፈሉበት ጊዜ ተጣሉ። በመንገድ ላይ ሲሄዱም ሰዎች አንድ የሬሳ ሳጥን ይዘው ሲጓዙ አዩ፤ አባ ጳውሊም የእኔም መጨረሻ ይኸው ነው! ወንድሜ ሆይ ከአንተ ጋር አልጣላም ብሎ ከኋላው ቀስ እያለ ተጓዘ፤ በመጨረሻም መንገዱን ቀይሶ ወደ በረሃ በመግባት በዓለም የመጀመሪያው ባህታዊ ሆኗል!

==> አባ እንጦንስም በቤተክርስቲያን ወንጌል ሲነበብ ሰማ፦ ፍጹም መሆን ብትፈልግ ያለህን ንብረት ሽጥና ተከተለኝ ማቴ [19: 22] የሚለውን ቃል ሰምቶ ያለውን ንብረት ሽጦ በዓለም የመጀመሪያ የሆነውን ገዳም በግብጽ ምድር መሰረተ!

==> እንደነ አብርሐም መርዓዊ ከጫጉላ ቤታቸው ወተው ገዳማዊ ህይወትን የኖሩ ታላላቅ አባቶች አሉ።

==> ገዳማዊ ህይወትን ለአባቶችችን ያስተማሩትም መድኃኒተ ዓለም ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ፤ ነቢዩ ኤልያስና መጥምቁ ዮሐንስ ናቸው።

No comments:

Post a Comment