Thursday, August 29, 2013

ዕለተ ሰኑይ /ሰኞ/

ዕለተ ሰኑይ /ሰኞ/

ጌታችንና መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሰው ሆኖ በዚህ ዓለም ሲመላለስ በሆሳዕና ማግሥት ጌታችን ከቢታንያ ወደ ኢየሩሳሌም ሲገባ ሁለት ነገሮችን አድርጓል፡፡ አንደኛ ከቅጠል በስተቀር ፍሬ ያልተገኘባትን ዕፀ በለስ ረግሟል፡፡ ሁለተኛ ወደ ቤተ መቅደስ ገብቶ የሚሸጡትንና የሚለውጡትን አስወጥቷል፡፡/ማቴ.21÷12-17፤ ማር.11÷17፤ ሉቃ.19÷45-46፡፡ በቅዱስ ሉቃስ ወንጌል ላይ እንደተገለጸው ይህንም ምሳሌ አለ "ለአንድ ሰው በወይኑ አትክልት የተተከለች በለስ ነበረችው ፍሬም ሊፈልግባት ወጥቶ ምንም አላገኘም፡፡" ሉቃ 13፡6 በማለት በበለስ ስለተመሰለ የሰው ልጅ ሕይወት በማሰብ እንዲመለስ ንስሐ እንዲገባ በሕይወትም እንዲኖር እግዚአብሔር ኢየሱስ ክርስቶስ ማሳሰቡን ያጠይቃል፡፡ ንስሐ አልገባም አልመለስም ያለም በለሷ እንደጠወለገችና እንደተቆረጠች ሁሉ ፍሬ ባለማፍራታቸው እንደሚቆረጡ እንዲሁም ወደ እሳት እንደሚጣሉ መጽሐፍ ቅዱስ በግልጽ ያስረዳል፡፡ በለስ የተባለች ቤተ እስራኤል ፍሬ የተባለ ደግሞ ሃይማኖትና ምግባርን ነው፡፡ ሁላችን ቤተ እስራኤላውያን ፍሬ ሃይማኖት ወምግባር አስተባብረን ይዘን መገኘት ይገባናል፡፡ ፍሬ አልባ እንዳንሆን ጌታ ሲመጣም እንዳናፍር የመጽሐፉን ቃል ልንጠብቅና ልንፈጽም ይገባናል፡፡ በዚህ የሕማማት የመጀመሪያ ቀን ዕለተ ሰኑይ የምናስበው የምንዘክረው የሰው ልጅ ሕይወት በከንቱ በቸልተኝነት እንዳይደክም እንዳይጠወለግ እንዳይደርቅ ወደ እሳትም እንዳይጣል ማድረግ ይገባናል፡፡

ጌታችን መድኃኒታችን ወደ ቤተ መቅደስ ግብቶ የሚሸጡትንና የሚለውጡትን እንዳስወጣ ሁሉ፤ ዛሬ የእግዚአብሔር ቤተሰቦች ጌታችን ወደ መቅደስ ሕይወታችን ቢመጣ ምን ያገኝ ይሆን? ፍሬ ወይስ ቅጠል? የእግዚአብሔር ቃል ግን ለንስሐ የሚገባ ፍሬ አድርጉ ይለናል። ማቴ 3፡8 ስለዚህ አምከ ቅዱሳን ከእኛ የሚፈልገውን የመንፈስ ፍሬ እናፍራ። ገላ 5፡22



የዛሬዋ ዕለት ጌታ የዕጸበለስን ዛፍ ፍሬ አይኑርብሽ ብሎ የረገመባት ቀን ነው በመባል ይታሰባል..ይህች በጌታ የተረገመችው ዕጸለስ ፀጋው የበዛላቸው ብዙ ሊቃውንት ተርጉመዋታል..አትሳደቡ ብሎ ህግን የሰራ አምላክ ተራጋሚ ሆኖ ሳይኖን ለማለት የፈለገው..በበለሷ በኩል ሊያስተምረን ያሰበው ነገር ይህነው..አይሁድ ሁሉን ትምህርቱን በሚገባ አስተምሮዋቸው ነበር..ትምህርቱ የቃል ብቻ ነው እንዳይሉ ደግሞ በተዐምራት የታገዘ ነብር..እግዚአብሄር እኔ ብርሃን ነኝ ብሎ ያስተምራቸውና እዛው ዓይን አብርቶ ያሳያቸዋል..ደግሞም እኔ የህይወት እንጀራ ነኝ ብሎ ያስተምራቸውና እዝያው ደግሞ እንጀራ አበርክቶ ያበላቸው ነበር..እኔ ትንሳኤና ህይወት ነኝ ብሎ ሞትን አሸንፏል..ይህንን የጌታ ምግባር የተመለከተው በ4ኛው መቶ ክ/ዘ የነበረው ሳዊሮስ የተባለው ሊቅ እንዲህ ይላል..እግዚአብሄር ትንሽ ነገር ተናግሮ ትልቅ ነገርን ያደርጋል..ሰዎች ግን ብዙ ትትለቅ ነገሮችን ይናገሩና ትንሿን ነገር እነኳን ማድረግ ያቅታቸዋል..ክርስቶስ ግን እኔ የዓለም ብርሃን ነኝ ማለቱ ትንሽ ነገር ነው ማንም ሊለው ይችላልና..ነገር ግን ዓይንነ አብርቶ ብርሃንን መፍጠር ለማንም አይቻልም..እኔ ትንሳኤና ህይወት ነኝ ማለት ቀላል ነገር ነው..ወደ ተግባር ሲመነዘር ግን ሙት ማስነሳትን ይጠይቃል.ህይወት ማደልን ይጠይቃል..ስለእዝህ ነው ሊቁ እግዚአብሄር ማንም ሊናገረው የሚችለውን ትንሽ ነገር ተናግሮ ትልቁን ነገር ያደርጋል ማለቱ..ስለሆነም አይሁድን በቃልም በተግባርም ካስተማረ በኃላ..ከእንገዲህ በኃላ ለሐጥያታችሁ ምክንያት የላችሁም..ስለሆነም በሊቃውንቱ አተረረጓገም በለሷን ክርስቶስ ፍሬ አይሁንብሽ ብሎ የተናገራት እስራኤላዊያንን ነው ይላሉ..ምክንያቱም ክርስቶስ በለሷን ሲያያት ቅጠሏ በጣም ያምራል..ነገር ግን ቀርቦ ሲያያት ፍሬ የላትም ቅጠሉ በራሱ የፍሬ ዋዜማ እንጂ ግቡ አይደለም..እስራኤላውያኑም ቢሆኑ ከሩቅ ሲያያቸው ብሉይ ኪዳንን ያምናሉ..የነብያቱን የነሙሴን ታሪክ ያውቃሉ..ለህጉም ተዠና ተቆርቋሪ ይመስላሉ..ቀረብ ብለው ሲያይዋቸው ምነም አይነት የዕምነት ፍሬ የለባቸውም..ስለእዚህ ነው በበለሷ በኩል አስታኮ ጌታ በሚስጥር ቤተ እስራኤላውያንን የተናገረው በማለት ሊቃውንቱ እነ ቅዱስ ዮሐነስ አፈወረቅ ሚስጥሩን ግልጽ ያደረጉት..ጌታም በመከጠል ወደ ቤተ መቅደስ ሄደ..ቤቱም የአምልኮ ቦታነቱ:የፀሎት ቦታነቱ:የወንጌል ቦታነቱ ቀርቶ ቅልጥ ያለ የገበያ አዳራሽ ሆኖ አገኝው..ጌታም ቤቴ የፀሎት ቤት ይባላል እናንተ ግን የወንበዴዎች ዋሻ አድርጋችሁታል ብሎ የሚሸጡትን ሁሉ ገለባበጠባቸው..እየገረፈም ከመቅደሱ አስወጣቸው..የህን ማድረጉ አንድም የቅዱስ መንፈሱ ማደርያ የሆነውን የእኛ የአዳም ልጆችን..ሐጥያት በቅደስ ሰውነታች ቆሽሾ ቢያገኝን ነውራችንነ ሁሉ እንዳራቀልን:እንዳፀዳን የሚገልጽ ነው..ከእዚህም የተነሳ አንጽሆተ ቤተ መቅደስ የተፈጸመባት ሰኞም ይባላል..በማስቀጠል የነገው ዕለት ማክሰኞ ነው

1


‹‹ሰሙነ ሕማማት››

‹‹ሰሙነ ሕማማት›› መጽሐፍ ቅዱሳዊ ሥርዓት ነው፡፡ በርካታ ሰዎች ቤተ ክርስቲያንን ከመጽሐፍ ቅዱስ ውጭ የምትጓዝ አካል አድርገው ሊገልጧት ይሞክራሉ፡፡ ይህ እጅግ አላዋቂ መሆናቸውን ይመሰክራል፡፡ ቤተ ክርስቲያን ከመጽሐፍ ቅዱስ ያልተገኘና በሥጋዊና በደማዊ ዕውቀት ላይ የተመሠረተ ሥርዓት የላትም፡፡ ቅዱስ ሉቃስ በሐዋርያት ሥራ ‹‹ከሕማማቱ በኋላ›› በማለት ስለ ሰሙነ ሕማማት የሚያወሳ ቃል ተጠቅሟል፡፡ (የሐዋ1.3)

ሰሙነ ሕማማት የሁለት ቃላት ጥምር ውጤት ነው፡፡ ‹‹ሰሙን›› የሚለው ቃል ‹‹ሰመነ›› ከሚለው የግዕዝ ቃል የተገኘ ሲሆን ስምንት ቀኖች ወይም ሳምንት ማለት ነው፡፡ ‹‹ሕማማት›› የሚለው ቃልም እንደዚሁ ‹‹ሐመመ›› ወይም ‹‹ሐመ›› ከሚለው የግዕዝ ቃል የተገኘ ሲሆን መከራዎች ማለት ነው፡፡ ‹‹ሕማማት›› የምንለው ለብዙ ሲሆን ነው፡፡ ለአንድ ወይም ለነጠላ ሲሆን ደግሞ ‹‹ሕማም›› እንላለን፡፡ እንግዲህ ሁለቱን ቃላት በማናበብ ‹‹ሰሙነ ሕማማት›› ስንል ‹‹የመከራዎች ሳምንት›› ማለታችን ነው፡፡

ሕማማት ስንል ምን ዓይነት ሕማም ወይም ምን ዓይነት መከራ? በማን ላይ? የሚሉት ጥያቄዎች ምላሽ ማግኘት አለባቸው፡፡ ሰዎች ልዩ ልዩ አደጋ ሲደርስባቸው መከራ አገኛቸው ይባላል፡፡ በሽታ ሲይዛቸውና በደዌ ሲሰቃዩ መከራቸውን አዩ እንላለን፡፡ ያላቸውን ሲያጡና ኪሣራ ሲደርስባቸው ሌላው ቀርቶ ሲርባቸውና ሥራ ሲበዛባቸው እንኳን ተሰቃዩ መከራቸውን አዩ ይባላል፡፡

በሰሙነ ሕማማት የምናስበው የኢየሱስ ክርስቶስ መከራ ከላይ ለሰው ልጆች ከጠቀስነውና ከተለመደው ዓይነት መከራ ይለያል፡፡ የተለየ ጊዜ ተወስኖለት ሰሙነ ሕማማት፣ ሕማማተ መስቀል፣ ሕማማተ ክርስቶስ ወዘተ እያልን በተለየ መንገድና ሥርዓት የምንገልጽውም ልዩ መከራ ስለሆነ ነው፡፡

ሕማማት የምንለው ኢየሱስ ክርስቶስ በእደ አይሁድ የተቀበለው የሐሰት ክስ፣ ፍርድ፣ መጎተት፣ መገረፍ፣ መገፈፍ፣ እርግጫ፣ ጥፊ፣ ጡጫ፣ ችንካር በአጠቃላይ በበርካታ ድርሳናት የተገለጠው አይሁድ የፈጸሙበትን ግፍ ሁሉ ነው፡፡ የአምላካችንና የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ መከራ በዓላማው፣ በአፈጻጸሙ፣ በመጠኑ፣ በምክንያቱ በአጠቃላይ በሁሉም መልኩ ከሰው ልጆች መከራ ጋር አይመሳሰልም፡፡

ነቢዩ ኢሳይያስ ወልደ እግዚአብሔር ኢየሱስ ክርስቶስን ‹‹የሕማም ሰው ደዌንም የሚያውቅ ነው፡፡›› ይለዋል፡፡ (ኢሳ53.3) ኢየሱስ ክርስቶስ መከራ የተቀበለው ስለእኛ ሲል ነው፡፡ በእኛ ላይ መድረስ የነበረበትን መከራ ሁሉ እርሱ ተሸከመልን፡፡ የእኛን ሞት ተቀብሎ የእርሱን ሕይወት ለእኛ ሰጠን፡፡ ይህን ሲያስረዳን ነቢዩ ኢሳይያስ ‹‹ሕመማችንንም ተሸክሞአል፡፡›› በማለት ጻፈልን፡፡ (ኢሳ53.4) ኢየሱስ ክርስቶስ መከራን የተቀበለው በፈቃዱ ነው፡፡

ኢየሱስ ክርስቶስ በፈቃዱ መከራን ተቀበለ ማለት ግን ግድሉኝ፣ ቸንክሩኝ አላቸው ማለት አይደለም፡፡ አይሁድ መከራ ሲያደርሱበት እነርሱን መቃወም፣ ማጥፋት፣ ወይም እንዳያገኙት ማድረግ ሲችል መከራን ተቀበለ ማለት ነው፡፡

ኢየሱስ ክርስቶስ እርሱ ስለ እኛ ብሎ የተቀበለውን መከራ እንድናስብ ይፈልጋል፡፡ ይህንንም አማናዊ ሥጋውንና ደሙን በሰጠን ጊዜ ‹‹ይህን ለመታሰቢያዬ አድርጉት›› በማለት አጽንቶ አዞናል፡፡ (ሉቃ22.19) ቅዱስ ጳውሎስ ስለ ሥጋውና ደሙ ባስተማረበት አጭር አንቀጽ ውስጥ ‹‹ለመታሰቢያዬ አድርጉት›› ያለውን ደጋግሞ የጠቀሰው ስለዚህ ነው፡፡ (1ቆሮ11.24፤ 1ቆሮ11.25) ሥጋውና ደሙ በመከራው ጊዜ የተሰጠን የሕይወት ስጦታ ነው፡፡ ስለዚህ በሥጋውና በደሙ መከራውን እናስባለን፡፡ ይህን ለማዘከር ቅዱስ ጳውሎስ ‹‹ሥጋውን በበላችሁ ደሙን በጠጣችሁ ጊዜ ዕለት ዕለት ሞቱን ትናገራላችሁ›› በማለት ጽፎልናል፡፡

በነገራችን ላይ ‹‹ዕለት ዕለት ሞቱን መናገር›› ማለት ሕማሙን ማሰብ ማለት ነው፡፡ ‹‹መናገር›› በመጽሐፍ ቅዱስ አስተምህሮ መሠረት ‹‹ማሰብ›› ሆኖ የሚተረጎምበት ጊዜ አለ፡፡ ሰው የሚናገረው የሚያስበውን ነውና፡፡ የልብ ሐሳብ በንግግር የሚገለጥ ስለሆነ መናገር የሐሳብ መገለጫ ወይም መዲና ነው፡፡ ማሰብ መነሻ ሲሆን መናገር መድረሻ በመሆናቸው እንደ አንድ ይታያሉ፡፡ ከዚህ የተነሳ መጽሐፍ ቅዱስ ስለ ማሰብ ለማውሳት ‹‹በልቡ እውነትን የሚናገር›› ይላል፡፡ (መዝ14.2) እስኪ መለስ ብላችሁ ጥቅሱን አስተውሉት ልብ ያስባል እንጂ ይናገራልን? ነገር ግን መናገር ከማሰብ ጋር ያለውን ጥብቅ አንድነት ለማሳወቅ መጽሐፍ ቅዱስ ቃላቶቹን በዚህ መንገድ አዘዋውሮ ይጠቀምባቸዋል፡፡ ሆነ ተብሎ እንጂ በስሕተት የተጻፈ እንዳልሆነ ልብ ይበሉ፡፡

ቤተ ክርስቲያን እነዚህን የመጽሐፍ ቅዱስ ቃላት አክብራ በመያዝ ዘወትር በቅዳሴ ሥጋውና ደሙን እያዘጋጀች ‹‹ንዜኑ ሞተከ እግዚኦ - አቤቱ ሞትህን እንናገራለን፡፡›› ትላለች፡፡ ‹‹አቤቱ ሞትህን እንናገራለን›› ማለትም ሁለት ዓይነት አፈታት አለው፡፡ አንዱ ግልጽና ቀጥተኛ ሲሆን ለሌላ ሰው ስለ ሞትህ እናውጃለን ማለት ነው፡፡ ሁለተኛው ደግሞ በላይኛው አንቀጽ እንደተረዳነው ሞትህን እናስባለን ማለት ነው፡፡

ቅዱስ ጳውሎስ እንደተናገረው አዚም ያለበት ሰው ካልሆነ በስተቀር እውነተኛ ክርስቲያን በልቡ ኢየሱስ ክርስቶስን እንደተሰቀለ ሆኖ ዘወትር ይመለከተዋል፡፡ (ገላ3.1) የአምላካችንን ሕማማት የምናስበው በቅዱስ ቃሉ መሠረት ‹‹ዕለት ዕለት›› ወይም ዘወትር ነው እንጂ በአመት ለአንድ ሳምንት ብቻ አይደለም፡፡
ለምሳሌ፡- የረቡዕና የዐርብ አጽዋማት የሕማማቱ መታሰቢያ ናቸው፡፡ በአንድ ዕለት ውስጥ የተመደቡት ሰባት የጸሎት ክፍለ ጊዜያት የሕማማቱ መታሰቢያ ሰዓታት ናቸው፡፡ እኩለ ሌሊት የተያዘበት፣ ማለዳ ለፍርድ የቆመበት፤ ሠለስት የተገረፈበት፣ እኩለ ቀን የተሰቀለበት፣ ዘጠኝ ሰዓት ቅድስት ነፍሱን ከክቡር ሥጋው በፈቃዱ የለየበት፣ ሠርክ ወደ መቃብር የወረደበት ሰዓታት በመሆናቸው ለሕማሙ መታሰቢያና ለጸሎት ጊዜነት ተመድበዋል፡፡
ይህም ብቻ አይደለም ቤተ ክርስቲያን ከሕማማቱ ጋር ያልተዛመደ ሥርዓት የላትም ማለት ይቻላል፡፡ ከበሮ፣ ጸናጽል፣ መቋሚያ ከሕማማቱ ጋር የተያያዘ ምሳሌነት አላቸው፡፡ ሁሉንም በዚህ ቦታ ማተት ጊዜ ይወስዳል፡፡ በምንዘምርበት ጊዜ ስናጨበጭብ በጥፊ መመታቱን፣ ስናሸበሽብ ደግሞ ወዲህ ወዲያ መንገላታቱን ወዘተ እያመላከትን ነው፡፡

ማኅሌቱ፣ ቅዳሴው፣ ሰዓታቱ፣ ዑደቱ ሁሉ ሕማማቱን እንድናስብ የሚያደርጉ ናቸው፡፡ በአጠቃላይ የቅዱስ ያሬድ መጻሕፍት፣ ዜማዎቹ፣ የዜማው ምልክቶች የኢየሱስ ክርስቶስን ሕማማት ለማሰብ በሚያግዝ መንገድ የተዘጋጁ ናቸው፡፡ የሕንጻ ቤተ ክርስቲያን አሠራርም ሕማማቱን ያዘክራል፡፡ በውስጥና በውጭ እንዲሁም በጉልላቱ ላይ መስቀል ማኖር ሕማማቱን እንጂ ሌላ ምን ያሳስባል? ከዚህም በተጨማሪ በቤተ ክርስቲያን ሕማማቱን የሚያሳስቡ ቅዱሳት ሥዕላት በየመልኩ ተስለው ይሰቀላሉ፡፡ከዚህ ሁሉ በተጨማሪ ቤተ ክርስቲያን የጌታችችን ሕማማት የምታስብበት ልዩ ሳምንት እና ልዩ ሥርዓት አላት፡፡ ወቅቱ ከዐቢይ ጾም ጋር ተያይዞ ባለው የመጨሻው ሳምንት ሲሆን ‹‹ሰሙነ ሕማማት›› ይባላል፡፡
የሕማማት ሳምንት የሚታወቅበት ልዩ ሥራ ደግሞ ጾም፣ ጸሎት፣ ስግደትና መጻሐፍትን ማንበብ ሲሆን ይህም ‹‹ግብረ ሕማማት›› ይባላል፡፡ በሰሙነ ሕማማት ሊሠራ የሚገባው ሥራ ማለት ነው፡፡ ይህን ሥርዓት ለማካሄድ የሚረዳው የቤተ ክርስቲያን መጽሐፍ እንደ ግብሩ ‹‹ግብረ ሕማማት›› ተብሏል፡፡

የጌታችን የመከራው መታሰቢያ እንዲደረግ የመጽሐፍ ቅዱስ ትእዛዝ መሆኑን ከላይ አብራርተናል፡፡ ያ ደግሞ እንዲሁ በዘፈቀደ የሚደረግ አይደለም፡፡ መጽሐፍ ቅዱስ ‹‹ሁሉ በአግባብና በሥርዓት ይሁን›› ይላልና፡፡ (1ቆሮ14.40) ቤተ ክርስቲያን በግብረ ሕማማት መጽሐፍ መሠረት ሕማማቱን የምትዘከረው በዚህ ምክንያት ነው፡፡

‹‹እንበለ ደዌ ወሕማም እንበለ ጻማ ወድካም አመ ከመ ዮም ያብጽሐኒ ወያብጽሕክሙ እግዚአብሔር በሰላም፡፡›› አሜን

Monday, August 26, 2013

በጎች እና ፍየሎች

አንድ ጊዜ በጎች እና ፍየሎች ከተለያየ አገር ለቅቀው ሲሄዱ ከሁለት ወገን የመጡት በጎች እና ፍየሎች አንድ ድልድይ ላይ ደረሱ፡፡ ድልድዩ ከወዲያ ወደዚህ ለመሻገር የሚቻለው በአንድ ጊዜ መሆኑን የድልድዩ ባለቤት ተናገረ፡፡ ከሁለቱም በኩል የመጡት በጎች በአንድ ላይ፣ ከሁለቱም በኩል የመጡት ፍየሎችም በአንድ ላይ፡፡
የሚያሳዝነው ግን ድልድዩ ሊያሳልፍ የሚችለው አንድ በግ ወይንም አንድ ፍየል ብቻ ነው፡፡ የሚፈቀደው ግን ከሁለቱም አቅጣጫ ሁለት በጎች ወይንም ሁለት ፍየሎች እንዲገቡ ነው፡፡
የመጀመርያው ዕድል ለፍየሎች ተሰጠ፡፡ ሁለት ፍየሎች ወደ ድልድዩ ከተለያየ አቅጣጫ ቀረቡ፡፡ እኔ ቀድሜ ማለፍ አለብኝ በሚል ሁለቱም ተጣሉና በቀንዳቸው መዋጋት ጀመሩ፤ በመጨረሻም ሁለቱም ወደ ወንዙ ወደቁ፡፡ ሌሎች ሁለት ፍየሎችም ሄዱ፡፡ እነዚህም ማን ይቅደም በሚለው ስላልተስማሙ ተዋጉ፡፡ ወንዝ ውስጥም ወደቁ፡፡
እንዲህ እንዲህ እያሉ ሁሉም ፍየሎች እየተዋጉ ወንዝ ውስጥ እየገቡ አለቁ፡፡
ቀጥሎም የበጎች ተራ ደረሰ፡፡ ሁለት በጎች ወደ ድልድዩ ከተለያየ አቅጣጫ ቀረቡ፡፡ ተነጋገሩ ተግባቡ፡፡ አንዱ በግ ተኛ ሌላው በላዩ ላይ አለፈ፡፡ ያኛውም ተነሥቶ አለፈ፡፡ እንደዚሁ ሌሎች በጎችም እየተነጋገሩ አንዱም እየተኛ፣ ሌላውም በላዩ ላይ እያለፈ፤ ያለምንም ችግር በጥቂት መቻቻል ተሻገሩ፡፡
ችግሮችን በመፍታት አካሄድ ይህ የበጎች እና የፍየሎች ሁኔታ እንዴት ይተረጎማል? በትዳር፣ በንግድ ሽርክና፣ በማኅበር፣ በድርጅት፣ በፓርቲ፣ በኮሙኒቲ፣ በቤተሰብ፣ ወዘተ ወዘተ፣ እንወያይበት

TEN COMMANDEMENT

All couples should read this. This is a good start to building a healthy and happy relationships.

Love is not just about finding the right person, but creating the right relationship.  It’s not about how much love you have in the beginning, but how much love you build until the end.  A relationship should be healthy, caring, loving, kind, upbeat, and positive.  It should make your smile a little wider and your life a little brighter.

Happy, healthy personal relationships are one of the greatest joys of life.  So starting today, choose to take control of your relationship with your significant other.  Here are ten commandments to follow together.

You deserve to be with somebody who makes you smile – somebody who doesn’t take you for granted somebody who won’t hurt you.

I.  We will remember that every person and relationship is different.

People don’t fall in love with what makes you the same; they fall in love with what makes you different.  Be your imperfectly perfect self.  We are not perfect for everyone, we are only perfect for those select few people that really take the time to get to know us and love us for who we really are.  And to those select few, being our imperfectly perfect self is what they love most about us.
Don’t compare your relationship to anyone else’s – not your parent’s, friend’s, coworker’s, or that random couple whose relationship seems perfect.  Every couple makes their own love rules, love agreements, and love habits.  Just focus on you two, and making your relationship the best it can be.

II.  We will listen to each other openly, without judgment.

It’s far too easy to look at someone and make a snap judgment about them.  But you’d be amazed at the pain and tears a smile hides.  What a person shows to the public is only a small fraction of the iceberg hidden from sight.  And more often than not, it’s lined with cracks and scars that run all the way to the foundation of their soul.

Never judge.  Learn to respect and acknowledge the feelings of your significant other.  Pay close attention to them.  Be present.  We don’t always need advice.  Sometimes all we need is a hand to hold, an ear to listen, and a heart to understand.  There is a time to speak out and a time to remain silent.  True wisdom comes from knowing the difference.  And this difference can make or break a healthy relationship.
 

III.  We will say what we mean and mean what we say.

Share what is going on in your mind and heart.  Share your deepest thoughts, needs, wishes, hopes, and dreams.  Open communication and honesty is vital to healthy relationships.  Give the people in your life the information they need, rather than expecting them to know the unknowable.

Information is the grease that keeps the engine of communication running.  Start communicating clearly.  Don’t try to read other people’s minds, and don’t make other people, especially your significant other, try to read yours.

IV.  We will support each other through good times and bad.

Be there through the good, bad, happy, and sad times – no matter what.  Be willing to provide a listening ear, a hug, and emotional support in all circumstances.  Trust that you can count on each other, and be available not only when it’s convenient, but when you need each other the most.

V.  We will be loyal.

True love and real friendship aren’t about being inseparable.  These relationships are about two people being true to each other even when they are separated.  When it comes to relationships, remaining faithful is never an option, but a priority.  Loyalty is everything.

VI.  We will live by the truth.

Inner peace is being able to rest at night knowing you haven’t used or taken advantage of anyone to get to where you are in life.  Lies run sprints, but the truth runs marathons.  Run a marathon.  Live so that when others think of fairness, integrity and reliability, they think of you.



VII.  We will spend quality time with each other.

Make time for each other.  With our busy schedules we often forget to relax and enjoy the great company we have.  In human relationships distance is not measured in miles, but in affection.  Two people can be right next to each other, yet miles apart.  So don’t ignore someone you care about, because lack of concern hurts more than angry words.

Carve out special time for just the two of you once a week.  Do something fun.  Spend time together talking, going on dates, and making each other laugh.  Not only is it true that laughter is the best medicine, but it’s also true that shared laughter can make a good relationship great.

VIII.  We will appreciate each other and help each other grow.

Having an appreciation for how amazing your significant other is leads to good places – productive, fulfilling, peaceful places.  So be happy for them when they’re making progress.  Cheer for their victories.  Celebrate their accomplishments, and encourage their goals and ambitions.  Challenge them to be the best they can be.  And be thankful for their blessings, openly.

IX.  We will settle disputes peacefully.

Not much is worth fighting about.  Heated arguments are a waste of time.  If you can avoid it, don’t fight.  Step back from arguments with your loved ones.

When you feel anger surging up and you want to yell that vulgar remark on tip of your tongue, just close your mouth and walk away.  Don’t let your anger get the best of you.  You don’t have to be right or win an argument.  It just doesn’t matter that much.  Give yourself some time to calm down and then gently discuss the situation.

X.  We will love and respect ourselves as individuals too.

Our first and last love is self-love.  Don’t rely on your significant other, or anyone else, for your happiness and self worth.  Only you can be responsible for that.  If you can’t love and respect yourself, no one else will be able to either.

Accept who you are completely – the good and the bad.  And make changes in your life as YOU see fit – not because you think anyone else wants you to be different, but because you know it’s the right thing to do, for you.

SEKOKAWE GIBTS

ሰቆቃወ ግብጽ ክርስትናን እሳት የሚያሸንፈው ቢሆን ኖሮ ድምጥያኖስና ዲዮቅልጥያኖስ በተሳካላቸው ነበር፡፡ ክርስትናን መግደል የሚያሸንፈው ቢሆን ኖሮ አይሁድና ሮማውያን፣ ኮሙኒስቶችና ማኦኢስቶች ድል በነሡት ነበር፡፡ ክርስትና በቤተ ክርስቲያኖች መቃጠል፣ በቅዱሳት መጻሕፍትም መቆነጻጸል የሚያበቃለት ቢሆን ኖሮ ኔሮንና ትራጃን፤ ዮዲት ጉዲትና ግራኝ ባስቆሙት ነበር፡፡ ክርስትና እሳት ሆኖ በእሳት ውስጥ ማለፍ ነው፡፡ ክርስትና እሳትን እሳት ሆኖ ድል መንሣት ነው፡፡ እዚህ እሳት ላይ ሦስቱ ሕጻናት ተጥለው ነበር፣ እዚህ እሳት ውስጥ ቂርቆስና እየሉጣ ተወርውረው ነበር፡፡ ይኼ እሳት ቅዱስ ፖሊካርፐስን በልቶት ነበር፡፡ ክርስትና ግን ይኼው አለ፡፡ ሊያጠፉት የተነሡት ሁሉ ተረት ሆነዋል፡፡ ክርስትና ግን ህያው ሆኖ አለ፡፡ የሠራነውን ቤተ ክርስቲያን ያቃጥሉ ይሆናል፣ የሠራነውን ሰማያዊ ቤት ግን አይደርሱበትም፡፡ ንብረታችንን ይወስዳሉ፣ እምነታችንን አያገኙትም፤ እኛን ይገድላሉ፤ ነፍሳችን ግን ከዐቅማቸው በላይ ናት፡፡ ይህንን መከራ አስቀድመን የማናውቀው ቢሆን ኖሮ በደነገጥን ነበር፡፡ ነገር ግን ክርስቲያን ስንሆን ይህ እንደሚመጣ እናውቅ ነበር፡፡ ‹ተዘጋጅታችሁ ተቀመጡ› ተብለናልና ተዘጋጅተን ነበር፡፡ እኛ ቆንጨራና ቦንብ፣ መትረጊስና አዳፍኔ አንይዝም፡፡ እኛ በጠጠር ጎልያድን የሚረታውን ይዘናል፡፡ በጩኸት ሳይሆን በዝምታ ኢያሪኮን የሚንደውን ይዘናል፡፡ በሁካታ ሳይሆን በርጋታ የሚሠራውን ይዘናል፡፡ እነርሱ ሲጮኹ ከአጋንንት ጋር ያወካሉ፤ እኛ ግን ዝም ስንል ከፈጣሪያችን ጋር እንነጋገራልን፡፡ ዛሬ በምድር ላይ የለኮሱትን እሳት ብዙዎች በሰማይ እነርሱው ይቀበሉታል፡፡ አይቀርም፤ አምላካችንም ዝም አይልም፡፡ እንገደላለን፤ ግን እናሸንፋለን፤ እንቃጠላለን፤ ግን እንለመልማለን፡፡ እናጣለን፤ ግን እናገኛለን፡፡ ቤተ ክርስቲያን ከተቃጠሉት ሕንጻዎቿ በላይ ናት