Sunday, July 27, 2014

ዮሐንስ በሥነ-ፍጥረት መመስሉ

ዮሐንስ በሥነ-ፍጥረት መመስሉ

1 ከአራቱ ኪሩቤል በገጸ ንሰር ይመሰላል ምክንያቱም፡-

❉ ንስር በእግሩ ይሸከረከራል በክንፉም ይበራል
ዮሐንስም ቀዳሚሁ ብሎ ሰማያዊን
ሥጋ ኮነ ብሎ ምድራዊ ልደቱን ጽፏልና

❉ ንሰር ከፍብሎ እንዲበር
ዮሐንስም ምሰጢረ መለኮት ተገልጦለት
ቀዳሚሁ ቃል…ብሎ ጽፏልና ነው

❉ አንድም ንስር ወደ ሰማይ መጥቆ ይበራል ወደ ምድርም ሲያይ ቅንጣት ታክል ሥጋ አታመልጠውም
ዮሐንስም አካል ከህልውና ተገልጦለት በንጽሐ ነፍስ ንጽሐ ሥጋ ንጽሐ ልቦና ተሰጥቶት
የቃልን ቀዳሚዊነትና ሥጋ መሆኑ ጽፏልና

2 ከአራቱ አፍላጋት በኤፍራጥሰ / በፈለገ ዘይት ይመስላል

❉ ዘይት/ወይራ ጽኑ ነው
ዮሐንስም ስለ ዓለም መከራና ከመከራውም ለመውጣት ብርቱ ጽናት
እንደሚያስፈልግ በመጻፉና ጽኑ እያለ በማስተማሩ /ዮሐ 16÷33/

❉ ዘይት በሩህ ነው

ወንጌላዊ ዮሐንስም በትምህርቱ የሰዎችን ልቡና ብሩህ ያደረገዋልና ነው

❉ አንድም ዘይት የሽቶ ዓይነቶችን ሰብስቦ አንድ ያደርጋል

ዮሐንስ የወንድሞቹን የወንጌላዊያንን ምሥጢር ጠቅልሎ በመጻፍ እንድ አድርጓቸዋልና ነው፡፡

3 ከአራቱ ባሕርያት ሥጋ በእሳት ይመሰላል

❉ እሳታዊ የሆነውን ነገረ መለኮትን አብዝቶ ጽፏልና ነው

4 ከ12ቱ እንቁዎች በአንዷ በመኀለቅ / መረግድ / ይመስላል፡፡
መኀለቅ ጠርዙ ሹል ስለታም ቀይ መልክ ያሉት ነው፡፡ /ራዕ. 21÷19 ትርጓሜ/

❉ ስለታም መሆኑ ሰማእታት በዚህ ዓለም መከራን ስለመቀበላቸው አብዝቶ ስለተነገረ ነው

❉ አንድም ሹል መሆኑ…ሹል በሆነ ነገር ድፍን የሆነውን ከፍተው እንደሚያወጡት ሁሉ
ለሃይማኖት ለምሥጢር ለዕውቀትና ለመጽሐፍ ድፍን የሆነ ልቡና ያላቸው መናፍቃንን
ድል የምነሳበት ሃይል ቃል አለውና ነው፡፡

❉ ቀይ እንደመሆኗ ለቤዛ-ዓለም እርሱ መድኀኔዓለም ደሙን እንዳፈሰሰ ጽፏልና ነው

5 ከአራቱ ወቅቶች መካከል በበጋ ይመስላል

❉ ይህ ወቅት መሬትዋ እሳት ላይ እንደተጣደ ብረት ምጣድ የምታቃጥልበት ነው
መሬቱ ደረቅ እንደሆነ ሁሉ ዮሐንስም ወንጌሉን መጻፍ ሲጀምር መናፍቃን ሊያጣምሙት የማይችሉትን
ደረቅ ቃል ነገረ መለኮትን አብዝቶ ጽፏልና ነው፡፡

6 ከአራቱ የያዕቆብ ሚስቶች በራሔል ይመስላል

❉ ያዕቆብ ከአራቱ ሚስቶቹ አብልጦ ይወዳት የነበረው ራሔልን ነው እንዲሁም ጌታ ከሌሎቹ ከደቀመዛሙርቱ ይልቅ ዮሐንስን ይወደው ነበርና ነው /የጌታ ወዳጅ ይለዋልን በመጽሐፍ/

❉ አንድም ራሔል በመጨረሻ ለያቆብ ልጁን እንደወለደችለት ሁሉ ዮሐንስም ወንጌሉን ከወንድሞቹ ኋላ /መጨረሻ/ ጽፏልና ነው
- ያዕቆብ …………….. የጌታ
- ልያና ራሔል ……….. የሐዋርያት ምሳሌ ናቸው፡፡
- ባለና ዘለፋ………….. የአርድእት

No comments:

Post a Comment